16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ 

የኤች አይ ቪ ፓዘቲቭስ በጎ አድራጎት ማህበራት ህብረት ለጤና እና ልማት (NAPHAD) 16ኛዉ መደበኛ የጠቅላላ ጉባኤ መጋቢት 18/2013 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ ያካሄደ ሲሆን በጉባኤዉም የሚከተሉትን አጀንዳዎች በመገምገም አጽድቋል

  • የስራ አመራር ቦርድ የ2020 ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2021 ዓመታዊ ዕቅድ
  • የህብረቱ የ2020 ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት
  • የህብረቱ የ2020 ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት
  • የህብረቱ የ2021 ዓመታዊ እቅድ

በመጨረሻም ጉባኤዉ ሲያገለግሉ የነበሩ የህብረቱ የቦርዶ አባላትን ስለነበራቸዉ አስተዋጾ የምስክር ወረቀት የሰጠ ሲሆን በተጨማሪም ተጨማሪ የዉጭ አካትን የቦርድ አባል ሆነዉ እንዲሰሩ ከተወያየ በኋላ በማስጸደቅ ጉባኤዉ ተጠናቋል፡፡